News page

ተማሪዎችን ማዕከል ያደረጉ የማነቃቂያ ንግግሮች ቀረቡ

[ሚያዝያ 2/2014 ዓ.ም፣ ባህር ዳር - ኢስኮ/ባቴኢ]የባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሙያ ማጎልበቻ ማዕከል ባሰናዳው ፕሮግራም ላይ በቅድሚያ ንግግር ያቀረቡት የTalent Firm መስራችና ዋና ሥ/አስኪያጅ ወ/ሪት ሩት ዮሃንስ ሲሆኑ በቀጣሪዎች ፍላጎት እና ተቀጣሪዎች እርከን መካከል ያለውን ልዩነት ከጥናታቸው ውጤት ጋር በማጣቀስ አቅርበዋል፡፡ እንደ ወ/ሪት ሩት ገለጻ ተማሪዎች በስራ ገበያው ተወዳዳሪ መሆን እንዲችሉ የቡድን ስራ፣ ችግር ፈቺነት፣ የፈጠራ ችሎታ፣ የማወቅ ፍላጎትና የተግባቦት ብቃታቸውን ከፍ ለማድረግ ዘወትር መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል፡፡

1ዐኛው ዓለም አቀፍ አውደ ጥናት በደማቅ የፋሽን ትርዒት ተጠናቀቀ

ለ10ኛ ጊዜ በጥጥ፤ጨርቃጨርቅ እና አልባሳት የእሴት ስንሰለት በአፍሪካ በሚል ርዕስ ጉዳይ ዓለም አቀፍ አውደ ጥናት በኢትዮጰያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጅ ኢንስቲትዪት አዘጋጅነት በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ አዳራሽ ሲካሄድ ቆይቶ በሠላም ግቢ ፋሽን አዳራሽ በደማቅ የፋሽን ትርዒት ተጠናቀቀ፡፡

Pages