የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ከፍተኛ የሥራ ጉብኝት አካሄደ

19 Nov, 2025

​ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ሕዳር 09/2018ዓ/ም)፣ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ በቦርዱ ሰብሳቢ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ የሥራ ጉብኝት አካሂዷል። ጉብኝቱ የዩኒቨርሲቲውን ወቅታዊ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ የትምህርት ግብዓቶች፣ የቴክኖሎጂ ማዕከላትን እና የተማሪዎችን የፈጠራ ሥራዎች በቅርበት ለመመልከት ያለመ ነበር።

የሥራ አመራር ቦርዱ ጉብኝቱን የጀመረው በኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BDU-EiTEX) ሲሆን፣ በውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ግንባታ፣ በአዳዲስ የማስተማሪያና የአስተዳደር ህንጻዎች ግንባታዎች እንዲሁም ቤተ-ሙከራዎችና የማስተማሪያ ፋብሪካዎች ላይ የተደረገውን ልማት አድንቋል። በተጨማሪም በአፓራል ፋኩልቲና በሥዕልና ቅርጻቅርጽ ተማሪዎች የተዘጋጁትን የፋሽንና የሥዕል አውደ-ርዕይ ተመልክቷል።

የተማሪዎች የስነ ምግባር አምባሳደር ለመለየት ውድድር ተካሄደ

12 Nov, 2025

የተማሪዎች የስነ ምግባር አምባሳደር ለመለየት ውድድር ተካሄደ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን በመወከል የስነ ምግባር አምባሳደር ለመሆን ከሁሉም ግቢዎች የተመለመሉ ተማሪዎች በዋናው ግቢ አዳራሽ ውድድር አካሄዱ፡፡
በውድድሩ ተገኝተው የፕሮግራም ትውውቅ ያደ

ለሆስፒታሎች ድጋፍ ተደረገ

05 Nov, 2025

 

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ከ partner in education Ethiopia ጋር በመተባበር ለሁለት ሆስፒታሎች የዓይን ህክምና መስጠት የሚያስችል ሙሉ የዓይን ህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ተደረገ ፡፡

በርክክብ ስነ ስርዓቱ የተገኙት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ተወልደ ውድነህ ዩኒቨርሲቲው የጉምሩክ ሂደትን ከማስፈፀም ባሻገር ሁሉንም የዓይን ህክምና መሳሪያዎች የቀረጥ ክፍያ ማለትም ከአራት ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ እንደፈፀመ ገልፀውልናል ፡፡

ማስታወቂያ

Submitted by TANA on

 

ለአቅም ማሻሻያ (Remedial) ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ :-

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በግል ከፍለው በማታው መርሀ-ግብር በአቅም ማሻሻያ (Remedial) መማር ለሚፈልጉ ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም በትምህርት ሚኒስትር የወጣውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጀምሮ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ ሰነዶች/ማስረጃዎች፣

● የትምህርት ማስረጃ ዋናውንና ፎቶ ኮፒ፤

● ለማመልከቻ የተከፈለበት ደረሰኝ (Application fee 300 ብር)

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁጥር፦1000224663378

የክፍያ መጠን፦ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች 4,480

ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች 3,720

የማመልከቻ ቦታ፦

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ኢንስቲትዩት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ

29 Oct, 2025


በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ኢንስቲትዩት መካከል በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም ተፈራረሙ ፡፡

የመግባቢያ ሰነዱ ዋና አላማ በኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ኢንስቲትዩት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መካከል የሥራ ግንኙነት መፍጠር ሲሆን ተዋዋይ ወገኖች የጋራ ፍላጎቶችን፣ መርኃ-ግብሮችን እና ተግባራትን በጋራ ለማቀድና ለመተግበር ይችሉ ዘንድ መረጃ እንዲለዋወጡ ማገዝ ነው ።

ይህ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ አስገዳጅ ያልሆነ፣ ነገር ግን መደበኛ የሆነ የጋራ ስልታዊ ጠቀሜታ ባላቸው መስኮች በጋራ ለመሥራት በተለይም በዓለም አቀፍ የብዝኃ-ሕይወት ስምምነቶች እና በብሔራዊ ልማት ዕቅዶች ውስጥ ኢትዮጵያ ለገባችው ቃል ኪዳን አስተዋፅዖ ለማድረግ ያላቸውን ፍላጎት ያሳያል።

ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ (በድጋሜ የወጣ)

Submitted by TANA on

ቀን፡ 18/02/2018 ዓ.ም

ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ (በድጋሜ የወጣ)

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት ለDiaster Risk Management and Food Security Studies አካዳሚክ ም/ዲን ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመሾም በወጣው ማስታወቂያ በቂ አመልካች ባለመገኘቱ በድጋሜ ማውጣት አስፈልጓል፡፡

ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡ ለDiaster Risk Management and Food Security Studies አካዳሚክ ም/ዲን

የማወዳደሪያ መስፈርት፡-

1ኛ. የትምህርት ማእረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት

BDU Alumni and Friends Donated 100k Birr Worth Books to EiTEX Community Library.

28 Oct, 2025

Alumni Stories: BDU Alumni and Friends Donated 100k Birr Worth Books to EiTEX Community Library.

Tibebe Ghion Specialized Hospital, in Collaboration with Israeli Specialists, Provides Advanced Laparoscopic Surgery Services

25 Oct, 2025


(October 25, 2025, Bahir Dar) — Tibebe Ghion Specialized Hospital, in collaboration with a team of specialist doctors from Israel led by Professor Hanoch Kashtan, has successfully provided advanced laparoscopic surgery services to patients.