Product Developers Registration - Wisdom Enterprise
Product Developers Registration - Wisdom Enterprise
የመመዝገቢያ ቅጹን ለማግኘት
17 Dec, 2025
17 Dec, 2025
Product Developers Registration - Wisdom Enterprise
የመመዝገቢያ ቅጹን ለማግኘት
12 Nov, 2025
05 Nov, 2025
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ከ partner in education Ethiopia ጋር በመተባበር ለሁለት ሆስፒታሎች የዓይን ህክምና መስጠት የሚያስችል ሙሉ የዓይን ህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ተደረገ ፡፡
በርክክብ ስነ ስርዓቱ የተገኙት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ተወልደ ውድነህ ዩኒቨርሲቲው የጉምሩክ ሂደትን ከማስፈፀም ባሻገር ሁሉንም የዓይን ህክምና መሳሪያዎች የቀረጥ ክፍያ ማለትም ከአራት ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ እንደፈፀመ ገልፀውልናል ፡፡
ለአቅም ማሻሻያ (Remedial) ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ :-
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በግል ከፍለው በማታው መርሀ-ግብር በአቅም ማሻሻያ (Remedial) መማር ለሚፈልጉ ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በትምህርት ሚኒስትር የወጣውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጀምሮ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ ሰነዶች/ማስረጃዎች፣
● የትምህርት ማስረጃ ዋናውንና ፎቶ ኮፒ፤
● ለማመልከቻ የተከፈለበት ደረሰኝ (Application fee 300 ብር)
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁጥር፦1000224663378
የክፍያ መጠን፦ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች 4,480
ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች 3,720
የማመልከቻ ቦታ፦
29 Oct, 2025
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ኢንስቲትዩት መካከል በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም ተፈራረሙ ፡፡
የመግባቢያ ሰነዱ ዋና አላማ በኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ኢንስቲትዩት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መካከል የሥራ ግንኙነት መፍጠር ሲሆን ተዋዋይ ወገኖች የጋራ ፍላጎቶችን፣ መርኃ-ግብሮችን እና ተግባራትን በጋራ ለማቀድና ለመተግበር ይችሉ ዘንድ መረጃ እንዲለዋወጡ ማገዝ ነው ።
ይህ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ አስገዳጅ ያልሆነ፣ ነገር ግን መደበኛ የሆነ የጋራ ስልታዊ ጠቀሜታ ባላቸው መስኮች በጋራ ለመሥራት በተለይም በዓለም አቀፍ የብዝኃ-ሕይወት ስምምነቶች እና በብሔራዊ ልማት ዕቅዶች ውስጥ ኢትዮጵያ ለገባችው ቃል ኪዳን አስተዋፅዖ ለማድረግ ያላቸውን ፍላጎት ያሳያል።
ቀን፡ 18/02/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ (በድጋሜ የወጣ)
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት ለDiaster Risk Management and Food Security Studies አካዳሚክ ም/ዲን ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመሾም በወጣው ማስታወቂያ በቂ አመልካች ባለመገኘቱ በድጋሜ ማውጣት አስፈልጓል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡ ለDiaster Risk Management and Food Security Studies አካዳሚክ ም/ዲን
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማእረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
28 Oct, 2025
Alumni Stories: BDU Alumni and Friends Donated 100k Birr Worth Books to EiTEX Community Library.